የብሪታኒያ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን አስታወቁ
የብሪታኒያ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ማት ሃንኮክ አርብ ዕለት በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን በቫይረሱ መያዛቸውን ከሰዓታት በኋላ አስታውቀዋል።
ሃንኮክ በትዊተር አካውንቱ ላይ በለጠፈው ቪዲዮ ላይ “ኮሮና እንዳለኝ ተረጋግጧል ፣ እና እንደ እድል ሆኖ ምልክቶቼ ቀላል ናቸው ፣ ከቤት እሰራለሁ እና እራሴን አገለያለሁ ።
ዛሬ ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን በቫይረሱ እንደተያዙ እና ቀላል ምልክቶች እያዩ መሆናቸውን ተናግረዋል ።
ራሱን እንዳገለለ እና ከቤት እንደሚሠራም አክሏል።
ልዑል ቻርልስ በቫይረሱ መያዛቸውም ከጥቂት ቀናት በፊት ተነግሯል።